+251463818559 info@amtvet.edu.et

በክልሉ ​ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እና ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ(ዶ/ር) የተመራ ልዑክ በአርባምንጭ ፖሊ-ቴክኒክ ሳታላይት እንስቲትዩት በተለያዩ ዘርፎች የሚከናወኑ የሥራ እንቅስቃሴዎችን ጎበኘ​

​የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አበባየሁ ታደሰ(ዶ/ር) የተመራ የልዑካን ቡድን በአርባ ምንጭ ከተማ ፖሊ-ቴክኒክ ኮሌጅ እና በሳተላይት ማዕከላት የሚከናወኑ የተለያዩ ሥራዎችን ተዘዋውሮ ተመልክቷል።በምልከታው ወቅት አበባየሁ(ዶ/ር) የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ለሀገር ዕድገት የጀርባ አጥንት በመሆኑ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። በክትትልና ቁጥጥር ወቅት...

አስደሳች ዜና ለአጫጭር ጌዜ ሥልጠና ፈላጊዎች በሙሉ

የአርባ ምንጭ ፖሊ-ቴክኒክና ሳተላይት ኢንስቲትዩት ከ Sustainable Employability and Entrepreneurship through Entrepreneurship Development (SEED) ጋር በመተባበር ማንኛውም ዕድሜው ለሥራ የደረሰ ዜጋ ሁሉ ከፍተኛ ልምድ ባላቸው አሰልጣኞችና በተደራጀ ወርክሾፕ በተለያዩ ሙያ ዘርፎች የአጫጭር ጊዜ ሥልጠና ለመስጠት ዝግጅቱን አጠናቅቋል ። የሥልጠና ዘርፎች ዝርዝር...

ለሚመልከታችሁ ባለሙያዎች በሙሉ

ኮሌጃችን አርባ ምንጭ ፖሊ ቴክኒክና ሳታላይት ኢንስቲትዩት ከዚህ በታች በተዘረዘሩ ሙያዎችና በሌሎች በልምድ ያገኙትን ክህሎት በተግባር ሥራ በመፈተሸ የእውቅና ሰርተፊኬት ባለቤት ለማድረግ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት በማጠናቀቅ እየተጠባበቀ ይገኛል፡፡ በልምድ ሊገኙ ይችላሉ ተብሎ የሚጠበቁ ዋና ዋና ሙያዎች ዝርዝር እንደሚከተለው...

በኢፌድሪ ሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ዘርፍ ሚኒስትር ደኤታ ዶ/ር ተሻለ በሬቻ የተመራ ልዑካን ቡድን በአርባ ምንጭ ፖሊ ቴክኒክና ሳታላይት ኢንስቲትዩት ጉብኝት አደረገ::

በኢፌድሪ ሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ዘርፍ ሚኒስትር ደኤታ ዶ/ር ተሻለ በሬቻ የተመራ የፌዴራልና የክልል የስራ ሃላፊዎች በአርባምንጭ ከተማና በጋሞ ዞን በዘርፉ የተከናወኑ ስራዎችን በሥፍራው ተገኝተው እየተመለከቱ ይገኛሉ። ልዑካን ቡድኑ በአርባ ምንጭ ፖሊ ቴክኒክና ሳታላይት ኢንስቲትዩት ጉብኝት ያደረገ ሲሆን፣ በቆይታቸውም የቴክኒክና ሙያ ስልጠናዎች፤​የተደራጁ ማህበራት እንቅስቃሴና የካይዘን...

የአርባምንጭ ፖሊቴክኒክ እና ሳተላይት ኢንስቲትዩት ለተማሪዎች, ለመምህራን እና ለሌሎች አሰተባባሪ ባለድርሻ አካላት በ 2018 ዓ.ም. አዲስ ገቢ ተማሪዎች ላይ የሚካሄደውን የሳይኮሜትሪክ ፈተና በሚመለከት ግንዛቤ ማስጨበጫ ሰጠ።

የአርባምንጭ ፖሊቴክኒክ እና ሳተላይት ኢንስቲትዩት ለተማሪዎች ለመምህራን እና ለሌሎች አሰተባባሪ ባለድርሻ አካላት በ2018 ዓ.ም. አዲስ ገቢ ተማሪዎች ላይ የሚካሄደውን የሳይኮሜትሪክ ፈተና (Psychometric TVET Placement System) በሚመለከት ግንዛቤ ማስጨበጫ ሰጠ። በተለይም የአካዳሚክ ጉዳዮች  ዋና ሃላፊ የሆኑት አቶ ሞላለኝ በቀለ በፕሮግራሙ መክፈቻ ላይ እንዳሉት በዚህ ወቅት የሳይኮሜትሪክ ፈተናው...

የአርባ ምንጭ ፖሊቴክኒክና ሳታላይት ኢንስቲትዩት በተለያዩ ሙያዎች 376 ተማሪዎችን አስመርቀ።

አርባ ምንጭ፣ ጥቅምት 01፣ 2018 (ዓ.ም) - የአርባ ምንጭ ፖሊቴክኒክና ሳታላይት ኢንስቲትዩት በተለያዩ የቴክኖሎጂ ሙያዎች 376 ሠልጣኞችን አሰልጥኖ በማስመረቅ የትምህርት ዘመኑን አጠናቋል። በማስመረቂያ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የተገኙት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቴክኒክና ሙያ ቢሮ ሰልጣኝ አሰልጣኝ ልማት ቢሮ ሃላፊ አቶ ዳዊት ፋንታዬ እንዳሉት ፣ እነዚህ ተማሪዎች በሀገራችን ኢንዱስትሪ እና ኢኮኖሚ ልማት ውስጥ ወሳኝ ሚና...

የ27ኛ ዙር ምሩቃን እንኳን ደስ አላችሁ❗

የአርባ ምንጭ ፖሊቴክኒክና ሳታላይት ኢንስቲትዩት ሥልጠና ከጀመረበት ከ1996 ዓ.ም. ጀምሮ ወቅታዊ የአካባቢያዊና ሀገራዊ የሰው ኃይል ገበያ ፍላጎት መሠረት አድርገው በሚቀያየሩ የሙያ ዓይነቶችና ደረጃዎች ብቁና ተወዳዳሪ የሆኑ ባለሙያዎችን ሲያፈራ የቆየ አንጋፋና ፈር ቀዳጅ ተቋም ነው፡፡ኢንስቲትዩቱ ማሠልጠን ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ ለዞናችን፣ ለአጎራባች ዞኖች፣ ለክልሉና ብሎም ለመላው ሀገሪቷ ልማት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ...

በክልል አቀፍ የፈጠራ፣ የቴክኖሎጂና የምርምር ውድድር የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ተወዳዳሪዎች እውቅና ተሰጣቸው።

‎የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቴክኒክና ሙያ ትምህርት ስልጠና ቢሮ "ብሩህ አዕምሮ፤በክህሎት የበቁ ዜጎች" በሚል መርህ ሀሳብ ያካሄደው የቴክኖሎጂ፣ የክህሎት እና የጥናትና ምርምር ውድድር ለአሸናፊዎች እውቅና በመስጠት ተጠናቅቋል። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቴክኒክና ሙያ ትምህርት ስልጠና ቢሮ ኃላፊ አቶ አብዮት ደምሴ በክህሎት፣ በቴክኖሎጂ እና በጥናትና ምርምር ዘርፎች የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ተወዳዳሪዎች ክልሉ እውቅና መስጠቱን...

በቴክኒክና ሙያ ተቋማት የሚፈጠሩ ቴክኖሎጂዎች የህብረተሰቡን ህይወት የሚቀይሩ መሆን እንዳለባቸው የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ቢሮ አስታወቀ::

የቴክኖሎጂ፣ የክህሎትና ተግባራዊ ጥናትና ምርምር ላይ ያተኮረ ክልል አቀፍ ውድድር በአርባምንጭ እና በወላይታ ሶዶ ከተሞች ተጀምሯል፡፡የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ሀገሪቱ የጀመረችውን የመበልፀግ ራዕይን በአዳዲስ ቴክኖሎጂዎች እያገዙ እንደሚገኙ ይነገራል፡፡የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ቢሮም በስሩ የሚገኙ የቴክኒክና ሙያ ተቋማትን በማደራጀት ብቁና ተወዳዳሪ ወጣቶችን ለመፍጠር በሚደረገው...

“ብሩህ አዕምሮዎች ፤የተፍታቱ እጆችና በክህሎት የበቁ ዜጎች” በሚል ርዕስ የቴክኖሎጂ፣ ክህሎት እና ምርምር ውድድር በአርባምንጭ ፖሊቴክኒክ እና ሳታላይት ኢኒስቲትዩት እየተካሄደ ይገኛል፡፡::

አርባምንጭ፣ መጋቢት 17/2017 ዓ.ም፡- የአርባ ምንጭ ክላስተር ያዘጋጀው የክህሎት፣ የቴክኖሎጂ እና ተግባራዊ የጥናትና ምርምር ውድድርና ኤግዚቢሽን በድምቀት እየተካሄደ ይገኛል፡፡ የጋሞ ዞን ዋና ዞን አስተዳዳሪ ደምስ አድማሱ (ዶ/ር) የቴክኒክና ዘርፍ በሀገራችን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ዕድገት አስተዋፅኦ የሚያበረክቱ ብቁና በሙያ የሚተማመን ዜጋ በመፍጠርና ድህነትን በመቀነስ ኢንዱስትሪያላይዜሽንን እውን ለማድረግ ተልዕኮ...